ዓርብ 3 ሜይ 2013

“እንሞታለን ገና” ጋዜጠኞች




            UNESCO ባወጣዉ ዘገባ አማካይነት በሳምንት አንድ ጋዜጠኛ እንደሚሞት ይፋ አድርጓል፡፡ የዚህ አንድ ጋዜጠኛ ህይወት የሚቀጠፈዉ ወይም ለመስዋዕትነት የሚቀርበዉ ለአድባር ወይም ለአምልኮ ጣዖት አይደለም፤
ለሙያዉ ክብር ሲል እንጂ፡፡ ይህ ጋዜጠኛ ሥራን ለመስራት ላይ ታች ሲል ህይወቱ በአንባገነኖች መዳፍ ዉስጥ ትወድቃለች፡፡
             በአለም አቀፉ ደረጃ የፕሬስ ነፃነት በሚከበርበት ዕለት በወጣዉ መረጃ መሰረት በፈረንጆች ዘመን አቆጣጠር ከ2006 እስከ 2012 ድረስ 502 ጋዜጠኞች የተገደሉ ሲሆን አሟሟታቸዉ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል፡፡መረጃዉም ከዚህ እንደሚከተለዉ ተቀምጧል፡-
ዘመን
የሟች ቁጥር
2006
70
2007
59
2008
48
2009
77
2010
65
2011
62
2012
121
  
          ይህ ድርጊት እየተፈፀመ ያለዉ በታዳጊ አገራት እና ዲሞክራሲ ባልተስፋፋባቸዉ አገሮች ብቻ አይደለም፡ ባደጉት አገሮችና ዲሞክራሲ ጥርሱን በነቀለባቸዉም አገራት ጭምር እንጂ፤ ይህ ደግሞ ለእንደ እኛ አገር  እጅግ ትልቅ ስጋት ነዉ፡፡
           ይህ መረጃ የሚያሳየን ይህቺ ዓለም ለጋዜጠኞችና ለኢየሱስ ክርስቶስ (አንዳች ሀሰት ያልተገኘበት) እንዳልተመቸች ነዉ

ሐሙስ 2 ሜይ 2013

‹‹እንደተናገረ ተነስቷል››



የዮሐንስ ወንጌል 20

1
ከሳምንቱም በፊተኛው ቀን መግደላዊት ማርያም ገና ጨለማ ሳለ ማለዳ ወደ መቃብር መጣች ድንጋዩም ከመቃብሩ ተፈንቅሎ አየች።


2
እየሮጠችም ወደ ስምዖን ጴጥሮስና ኢየሱስ ይወደው ወደ ነበረው ወደ ሌላው ደቀ መዝሙር መጥታ። ጌታን ከመቃብር ወስደውታል ወዴትም እንዳኖሩት አናውቅም አለቻቸው።


3
ስለዚህ ጴጥሮስና ሌላው ደቀ መዝሙር ወጥተው ወደ መቃብሩ ሄዱ።


4
ሁለቱም አብረው ሮጡ፤ ሌላው ደቀ መዝሙርም ከጴጥሮስ ይልቅ ፈጥኖ ወደ ፊት ሮጠና አስቀድሞ ከመቃብሩ ደረሰ፤


5
ዝቅም ብሎ ቢመለከት የተልባ እግሩን ልብስ ተቀምጦ አየ፥ ነገር ግን አልገባም።


6
ስምዖን ጴጥሮስም ተከትሎት መጣ ወደ መቃብሩም ገባ፤ የተልባ እግሩን ልብስ ተቀምጦ አየ፥


7
ደግሞም በራሱ የነበረውን ጨርቅ ለብቻው በአንድ ስፍራ ተጠምጥሞ እንደ ነበረ እንጂ ከተልባ እግሩ ልብስ ጋር ተቀምጦ እንዳልነበረ አየ።


8
በዚያን ጊዜ አስቀድሞ ወደ መቃብር የመጣውም ሌላው ደቀ መዝሙር ደግሞ ገባ፥ አየም፥ አመነም፤


9
ከሙታን ይነሣ ዘንድ እንዲገባው የሚለውን የመጽሐፉን ቃል ገና አላወቁም ነበርና።


ደቀ መዛሙርቱም ወደ ቤታቸው ደግሞ ሄዱ።


ማርያም ግን እያለቀሰች ከመቃብሩ በስተ ውጭ ቆማ ነበር። ስታለቅስም ወደ መቃብር ዝቅ ብላ ተመለከተች፤


ሁለት መላእክትም ነጭ ልብስ ለብሰው የኢየሱስ ሥጋ ተኝቶበት በነበረው አንዱ በራስጌ ሌላውም በእግርጌ ተቀምጠው አየች።


እርሱም፦ አንቺ ሴት፥ ስለ ምን ታለቅሻለሽ? አሉአት። እርስዋም፦ ጌታዬን ወስደውታል ወዴትም እንዳኖሩት አላውቅም አለቻቸው።


ይህንም ብላ ወደ ኋላ ዘወር ስትል ኢየሱስን ቆሞ አየችው፤ ኢየሱስም እንደ ሆነ አላወቀችም።


ኢየሱስም፦ አንቺ ሴት፥ ስለ ምን ታለቅሻለሽ? ማንንስ ትፈልጊያለሽ? አላት። እርስዋም የአትክልት ጠባቂ መስሎአት። ጌታ ሆይ፥ አንተ ወስደኸው እንደ ሆንህ ወዴት እንዳኖርኸው ንገረኝ እኔም እወስደዋለሁ አለችው።


ኢየሱስም፦ ማርያም አላት። እርስዋ ዘወር ብላ በዕብራይስጥ።

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

የቀኝ ዐይን - ድንግል ማርያም

  የቀኝ ዐይን - ድንግል ማርያም   ( በዲ / ን ብርሃኑ አድማስ ) አፍጣኒተ ረድኤት ማርያም በጊዜ   ምንዳቤ ወአጸባ ለዐይን እምቀራንባ፤ አንቲ ውእቱ ረዳኢተ ያዕቆብ በቤተ ላባ፤ በኩ...